ዓርብ 25 ጁላይ 2014

መላኩ ቅዱስ ገብርኤል በሐሙሌ 19 የሠራው ተዐምር

እንኮን ለሊቀ መላእኩ ቅዱስ ገብርኤል አመታዊ ክብረ በዐል       በሰላም አደረሳችሁ

መላኩ ቅዱስ ገብርኤል #በእግዚአብሔር ትእዛዝ በሐሙሌ 19 የሠራው ተዐምር ይሕ ነው

እለ እስክንድሮስ የተባለ መኰንን በኢየሱስ ክርስቶስ ያመኑትን
ክርስቲኖች ለመቀጣትና ሌሎችም ፈርተው ክርስትናን
እንዳይፈልጉ ለማድረግ አስቦ ሰም፣ ጨው፣ ባሩድ፣ ሙጫ፣
የዶሮ ማር፣ እርሳስ፣ ብረት፣ ቅንጭብ፣ ቁልቋል አንድ ላይ
ተቀላቅሎ በብረት ጋን እንዲፈላ አዝዞ ነበር፡፡ ጭፍሮቹም
እለስክንድሮስ እንዳዘዛቸው ከአደረጉ በኋላ ያዘዝኸንን ሁሉ
ፈጽመን እሳቱ ነዶ ፈልቷል፤ ድምፁ እንደነጐድጓድ ይጮሃል፤
ወላፈኑም እንደ ፀሐይ ነፀብራቅ በሩቅ ይጋረፋል፤ የፍላቱም
ኀይል አሥራ ዐራት ክንድ ያህል ከፍታ ወደላይ ይዘላል፤
እንግዲህ በውስጡ የሚጣሉትን እዘዝ አሉት፡፡
በዚህ ጊዜ ሕፃን ቂርቆስና እናቱ ኢየሉጣ በክርስቶስ ስም
ስለሚያምኑ አሥረዋቸው ነበርና ከፍላቱ ሊጨምሯቸው
ከእሥር ቤት አወጧቸው፡፡ ፍላቱ ወደ ላይ በሚዘል ብረት ጋን
ውስጥ ለመጨመር ሲወስዷቸው የእነዚህን ቅዱሳን
አሟሟት ያዩ ዘንድ በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ ሰዎች እንዲሰበሰቡ
ታዘዘ፡፡
በዚህ ጊዜ ቅድስት ኢየሉጣ የፍላቱን ጩኸት በሰማችና ባየች
ጊዜ ተሸበረች፤ ተዘጋጅቶላት ከነበረውም ክብር ልታፈገፍግ
ሞከረች፡፡
ልጅዋ ቅዱስ ቂርቆስ ግን እናት ሆይ ከዚህ የብረት ጋር
ግርማ የተነሣ አትፍሪ፤ ድንጋፄም አይደርብሽ፤ አናንያንና
አዛርያን፣ ሚሳኤልንም #እግዚአብሔር ከዕቶነ አሳት
እንዳወጣቸው ሁሉ እኛንም ከዚህ ከብረት ጋን ሊያወጣን
ችሎታ ያለው መሆኑን አትጠራጠሪ ፡፡ እናት ሆይ ከዚህ
ከሚያልፈው ዓለም ጭንቅና መከራ ለማዳን ስትይ
በማያልፈው በዘለዓለም እሳት ለመቀጣት ትመርጫለሸን?
ይህስ አይሆንም፤ ይቅርብሽ፤ በአሁኑ ጊዜ #እግዚአብሔር
በመካከላችን አለና ይረዳናል፡፡ እናቴ ሆይ ሶስናን ከእደ
ረበናት፣ /መምህራነ አይሁድ/ ዳንኤልን ከአፈ አናብስት ያዳነ
እሱ እኛንም ከዚህ የጋን ፍላት ያወጣናል፡፡ ይልቁንም
#እግዚአብሔር በዚህ የብረት ጋን ውስጥ ግዳጃችንን ልንፈጽም
ፈቅዶ ከሆነ ኢዮብ ንብረቱንና ገንዘቡን፣ ልጆቹንና ሚስቱን፣
በመጨረሻም የተፈጥሮ አካሉን ባጣ ጊዜ እግዚአብሔርን
አመሰግነዋለሁ፤ እግዚአብሔር ሰጠ፤ #እግዚአብሔር ነሣ፤ /
ወሰደ/ #እግዚአብሔርም እንደ ወደደ አደረገ፤ ከማለት
በስተቀር ምንም የተናገረው ክፉ ነገር እንደሌለ ሁሉ እኛም
የሱን ዓላማ በመከተል ይህን መከራ ልንታገሥ ይገባናል፤
አላት፡፡
ነገር ግን እናቱ ቅድስት ኢየሉጣ በዚህ ምክር ልትጽናና
ባለመቻሏ ቅዱስ ቂርቆስ ዓይኑን ወደ ሰማይ አቅንቶ አቤቱ
አምላኬ ሆይ ይህችን ባሪያህን ከርስትህ የምትለያት ከሆነ
ከባለሟልነትህ መጽሐፍ ፋቀኝ፤ አቤቱ አዝመራውን አቃጥለህ
ፍሬውን ልትባርክ ትወዳለህን ይህን እንዳታደርግ ግን ቸርነትህ
ትከለክልሃለች፡፡
አቤቱ እንጨቱን ቆርጣችሁ አንድዱት፤ ቅጠሉን ግን
ጠብቁት፤ ብለህ ልታዝ መለኮታዊ ባሕርይህ አይደለም፤ ነገር
ግን እንጨቱንም ቅጠሉንም ባንድ ጠብቁት፤ ብለህ ታዝዛለህ
እንጂ፤ እንግዲህ በዚህ ምክንያት ይህን ያየ ሁሉ ማዳን
የሚችል አምላክ ቢኖራቸውስ ኖሮ ከዚህ ከእሳት ባልሸሹም
ነበር ብሎ አይጠራጠር፡፡
አቤቱ ዲያብሎስም ከባለሥልጣኑ ይልቅ እኔ በረታሁ፤
ቅዱሳኖቹንም ድል ነሣኋቸው፤ ብሎ እንዳይመካ ከመንጋውም
አንድ በግ ቀማሁ፤ በማለት እንዳይደነፋ ለናቴ ጽኑ የሆነ ኃይለ
መንፈስ ቅዱስን ስጣት፤ ብሎ በጸለየ ጊዜ ዲያብሎስ ከኢየሉጣ
አጠገብ ብን ብሎ ጠፋ፡፡
ከዚህ በኋላ ቅድስት እናቱ በሰማያዊ መንግሥት አባት
የሆንከኝ ልጄ ሆይ ጌታህ ኃይልን ሰጥቶኛልና የሚጠብቀንን
ገድላችንን ፈጽመን ድል እናድርግ፤ እነሆ በብረት ጋኑ ውስጥ
የሚነደውን እሳት በማይበት ጊዜ በለምለም /በምንጭ/ ላይ
እንደሚወርድ ጠል ሆኖ አይቼዋለሁና አለችው፡፡
እኒህም ቅዱሳን ይህን በሚነጋገሩበት ጊዜ በውስጡ አንገትን
የሚቆለምም፣ ልብን የሚያቀልጥ፣ ሆድን የሚሠነጥቅ፣
ሥርን የሚበጣጥስ መሣሪያ ካለበት የብረት ጋን ውስጥ
ጨመሯቸው፡፡ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ገብርኤል ከሰማይ
ወረደና የብረቱን ጋን እሳት አጠፋው፤ ከቅዱሳኑም
አንዳቸውንም ሳያቃጥላቸው የብረቱ ጋን ማቃጠሉና
መፍላቱም ፀጥ አለ፡፡
ዳግመኛም እለ እስክንድሮስ ሀሳቡ ሳይሳካለት ስለቀረ አሥራ
አራት የሾሉና የጋሉ የብረት ችንካሮች አምጥተው ሰባቱን
በእናቱ በኢየሉጣ አካል፣ ሰባቱን በቂርቆስ አካል ይቸነክሯቸው
ዘንድ ጭፍሮቹን አዘዘ፡፡
ዳግመኛም የሕፃንን የእራስ ቆዳ ገፈው እሳት ውስጥ
ይጨምሩት ዘንድ አዘዘ፡፡ አሁንም መልአኩ መጥቶ ይህን
መከራ አራቀለት፡፡ ቀጥሎም በመቃን ውስጥ ጨምረው
በገመድ እንዲጎትቱት አዘዘ፤ በዚህም ጊዜ መልአኩ አዳነው፡፡
ሕዝቡም ይህን ሁሉ ተአምር በአዩ ጊዜ እግዚአብሔርን
አመሰገኑት፤ ቅዱስ ገብርኤልንም አከበሩት፡፡

ከበዐሉ ረድኤት በረከት ተካፋይ እንድንሆን አምላካችን ልውል #እግዚአብሔር ይርዳን

እሑድ 23 ማርች 2014

                                                   የዐቢይ ጾም 5ኛ ሳምንት

       የዐቢይ ጾም 5ኛ ሳምንት
              ደብረ ዘይት- የምጽአት መታሰቢያ
        ደበረ ዘይት

"የሚያስታችሁ እንዳይኖር ተጠንቀቁ፡፡ ብዙዎች እኔ ክርስቶስ
ኝ     እያሉ በስም ይመጣሉ ብዙዎችንም ያስታሉ" ማቲ፡24፡5-8
ያብይ ጾም አምስትኛ ሳምንት ደብረዘይት ነው፡፡

ደብረዘይት የጾም እኩልታ ነው ትርጉሙም ደብር ማለት ተራራ ዘይት ደግሞ የወይራ ዘይት የሞላበት ቦታ ነው:: ቦታው ከምስራቅ እየሩሳልም ከጎሎጎታ ተራራ በግምት ሁለት ኪሎ ሜትር እርቀት አለው ::

በዚህም ቦታ መድሃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዘመነ ስጋዊ ጉዞ በደብረ ዘይት ተራራ ያልፍ እንደነበርና እንዳስተማረ መጽሐፍ ቅዱስ ያስረዳል ማቴ-24:1-36
 
                                                        

በዚህም ተራራ ስለ አለም ምጽአት ስለዳግም መምጣቱም አስተምሮአል ክርስቶስ ስለዳግም ምጽአቱ ባስተማረ ጊዜ
ለደቀ መዛሙርቱ
        “ይህን ሁሉ ታያላችሁን ዲንጋይ በዲንጋይ ላይ ሳይፈርስ   በዚህ   አይቀርም'' ማቴ 24፡2-3

አላቸው ደቀ መዛሙረቱም ስለአለም ፈጻሜ ምልክተ ጠየቁት ክርሰቶስም ስለመምጣቱና ምልክቱን ነገራቸው

ዲንጋይ በዲንጋይ ላይ ይፈርሳል
ብዙዎች እኔ ክርስቶስ ነኝ ብለው ይነሳሉ
ጦርነትና የጦርነት ወሬ ይሰማል
ህዝብ በህዝብ ላይ መንግስትም በመንግስት ላይ ይነሳል
በዙዎችም ሀይማኖታቸውን ይለውጣሉ
ቸነፈርና የምድርም መናወጥ ይሆናል

መድሃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዘመነ ስጋዊ ጉዞ በደብረ ዝይት ተራራ ስልአለም ፍጻሜ ያስተማራቸው ትምህርቶች የምጽአቱ ምልክቶች ዲንጋይ በዲንጋይ ላይ ይፈርሳል
ብዙዎች እኔ ክርስቶስ ነኝ ብለው ይነሳሉ
ጦርነትና የጦርነት ወሬ ይሰማል
ህዝብ በህዝብ ላይ መንግስትም በመንግስት ላይ ይነሳል
በዙዎችም ሀይማኖታቸውን ይለውጣሉ
ቸነፈርና የምድርም መናወጥ ይሆናል

ዛሬ በዘመናችን እየተነሱ ናቸው ::
ብዙዎችም ሃይማኖታቸውን ከመለወጣቸው የተነሳ ዛሬ ለቁጥር የሚያስቸግሩ ሃይማኖቶች በምድራችን ላይ ይገኛሉ መጽሐፍ ቅዱስም እንዲህ ይላል

''ከነዚህ ቀኖች መከራ በኋላ ወዲያውኑ ጸሀይ ይጨልማል ጨረቃም ብርሃኑን አይሰጥም ክዋክብቱም ከሰማይ ይወድቃሉ የሰማያት ኃይልም ይናወጣል'' ማቴ 24፡29-30



የዕለተ ሰንበት መዝሙር (ከጾመ ድጓ

እንዘ ይነብር እግዚእነ ውስተ ደብረ ዘይት ወይቤሎሙ ለአርዳኢሁ ዑቁኬ ኢያስሕቱክሙ ወንበሩ ድልዋኒክሙ ብዙኃን ይመጽኡ በስምየ እንዘ ይብሉ አነ ውእቱ ክርስቶስ ወዘአዝለፈ ትዕግሥቶ ውእቱ ይድኅን ወአመ ምጽአቱሰ ለወልደ እጓለ እመሕያው ይትከወስ ኲሉ ኃይለ ሰማያት ወምድር አሜሃ ይበክዩ ኲሎሙ ኃጥአነ ምድር፡፡ ወይወርድ እግዚእነ እምሰማይ ዲበ ምድር በትእዛዙ ወበቃሉ ወበ አዕላፍ መላእክቲሁ በንፍሐተ ቀርን ዘእም ኀበ እግዚአብሔር ይምሐረነ አብ በይእቲ ሰዓት እሞተ ኃጢአት እስመ ገባሬ ሕይወት ውእቱ እግዚኣ ለሰንበት፡፡

ትርጉም:- ጌታችን በደብረ ዘይት ተራራ ላይ ተቀምጦ ሳለ ለደቀ መዛሙርቱ ማንም እንዳያስታችሁ ተጠንቀቁ፤ተዘጋጅታችሁም ኑሩ፤ብዙዎች እኔ ክርስቶስ ነኝ እያሉ በስሜ ይመጣሉ፤ እስከ መጨረሻው የጸና እርሱ ይድናል፡፡ የሰው ልጅ በሚመጣበት ጊዜ የሰማያትና የምድር ኃይላት ሁሉ ይናወጣሉ።ያን ጊዜ በምድር ኃጢአት ያደረጉ ሁሉ ያለቅሳሉ አላቸው፡፡ጌታችንም ከባሕርይ አባቱ ከእግዚአብሔር አብ ዘንድ በመለከት ድምፅ ከአእላፍ መላእክት ጋር በግርማ መለኮቱ ከሰማይ ወደ ምድር ይወርደል፡፡ በዚች ዕለትም ከሞተ ኃጢአት አብ ይማረን የሕይወት ባለቤት የሰንበትም ጌታ ነውና፡፡

ምንባባት መልዕክታት
(1ኛተሰ.4÷13-ፍጻ.) ወንድሞቻችን ሆይ÷ ስለ ሞቱ ሰዎች÷ ተስፋ እንደሌላቸው ሰዎች እንዳታዝኑ ልታውቁ እንወዳለን፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስ ሞቶ እንደ ተነሣ ካመንን እንዲሁ እግዚአብሔር ሙታንን በኢየሱስ ያስነሣቸዋል፤ ከእርሱም ጋር ያመጣቸዋል፡፡ .......
(2ኛ ጴጥ.3÷7-14) አሁንም ሰማይና ምድር በዚያ ቃል ለእሳት ተዘጋጅተዋል፤ ኃጥኣን ሰዎች እስከሚጠፉበት እስከ ፍርድ ቀንም ተጠብቀዋል፡፡ነገር ግን ወንድሞቻችን ሆይ÷ ይህን አትርሱ፤ በእግዚአብሔር ዘንድ አንዲት ቀን እንደ አንድ ሺህ ዓመት÷ ሺህ ዓመትም እንደ አንድ ቀን ነውና፡፡

ግብረ ሐዋርያት
(የሐዋ. 24÷1-21) በአምስተኛውም ቀን ሊቀ ካህናቱ ሐናንያ ከመምህራኑና ጠርጠሉስ ከሚባል አንድ ጠበቃ ጋር ወረደ፤ ጳውሎስንም በአገረ ገዢው ዘንድ ከሰሱት፡፡ ጳውሎስም በቀረበ ጊዜ ጠርጠሉስ እንዲህ እያለ ይከስሰው ጀመረ፤ “ክቡር ፊልክስ ሆይ÷ በዘመንህ ብዙ ሰላምን አግኝተናል፤ በጥበብህም በየጊዜው በየሀገሩ የሕዝቡ ኑሮ የተሻሻለ ሆኖአል፤ ሥርዐትህንም በሁሉ ዘንድ ስተመሰገን አግኝተናታል፡፡(ተጨማሪ ያንብቡ)

ምስባክ
መዝ. 49÷2 እግዚአብሔርሰ ገሃደ ይመጽእ፡፡ ወአምላክነሂ ኢያረምም፡፡ እሳት ይነድድ ቅድሜሁ፡፡

ትርጉም፦ እግዚአብሔር በግልጥ ይመጣል፡፡ አምላካችንም ዝም እይልም፤ እሳት በፊቱ ይነድዳል በዙሪያውም ብዙ ዐውሎ አለ፡፡

ወንጌል
(ማቴ. 24÷1-25)

ቅዳሴ: - ቅዳሴ ዘአትናቴዎስ



      ''ይህ ሊሆን ግድ ነውና ተጠንቀቁ አትደንግጡ ነገር  ግን ፍጻሜው    ግና ነው''
ማቴ 24፡6-7